የናፈቅከኝ ለታ This is for you Betsi .... this poem speaks my heart ... hope it will also speaks yours
የናፈቅሽኝ ለታ ብለሽ አንብቢው thank you Mes Demoz
##### የናፈቅከኝ ለታ…#####
---------------------------------
የናፈቅከኝ ለታ…
ሳር ቅጠሉ ሁሉ አንተን ይመስለኛል
ከፊት ከኋላዬ ጎኔ የተቀመጥክ መስሎ ይሰማኛል።
ሳር ቅጠሉ ሁሉ አንተን ይመስለኛል
ከፊት ከኋላዬ ጎኔ የተቀመጥክ መስሎ ይሰማኛል።
የናፈቅከኝ ለታ…
የድምፅሕ ወለለት…
በእኩለ ሌሊት ገዝፎ ይሰማኛል፣
ባንቀላፋሁበት…
እንደ ዶሮ ጩኸት፣
እንደ ደብር ደውል፣
እንደ ወፍ ዝማሬ፣ ይቀሰቅሰኛል።
የናፈቅከኝ ለታ…
የሞቀው አልጋዬ…
እንደ ምድር ዋልታ
እንደሙት ሰውነት
እንደደጋን ቆፈን ይቀዘቅዘኛል፣
ለስላሳው አንሶላ
እንደ ደረቅ ቁርበት ይኮሰኩሰኛል።
የተመቸው ነገር ምቾት አይሰጠኝም፣
የጣፈጠው ምግብ
ጣዕሙ አይገባኝም።
( ውሃ እንኳ ያንቀኛል።)
አይገርምም?!
የናፈቅከኝ ለታ…
ጨዋታው ለዛ ቢስ
ሙዚቃው ሁካታ
ፀሐይዋ በረዶ
ቅዝቃዜው እቶን ሆኖ ይሰማኛል፣
ከተፈጥሮ አጋጭቶ
ከሰውኛ ህግጋት ገፍቶ ያስወጣኛል።
የናፈቅከኝ ለታ…
የጨረቃ ውበት አይስብ አይማርከኝ
የከዋክብት ብርሃን ከሉን አይገፍልኝ
ብቻ አንተን ብቻ አንተን አንተን እላለሁኝ።
ዳሩ ምን ዋጋ አለው…
ፀጉርህን ዳብሼ አቅፌ እንዳልስምህ
ድምፅህን እንዳልሰማ ናፍቄ እንዳላይህ
እልፍ ርቀኸኛል!
ህልም ሆነህብኛል!
ቢሆንም…
ወድሃለሁና ትናፍቀኛለህ
በሠዓት በደቂቃ ትዝ ትለኛለህ።
`ወድሃለሁና እናፍቅሃለሁ
ያውም ደስ እያለኝ፣
ተስፋ አለኝ ባንተ ደርሰህ እስክታክመኝ።
ደግሞ…እጠብቅሃለሁ!
ተከተይኝ በለኝ…
እስከዓለም ጥግጋት…
እስከዓለም ፍፃሜ…
ማቄን ጨርቄን ሣልል…እከተልሃለሁ!
ትናፍቀኛለህ…ውዴ…እወድሃለሁ!
* Mes Demoze
( ጥር 21 ቀን 2005 ዓ.ም)
የድምፅሕ ወለለት…
በእኩለ ሌሊት ገዝፎ ይሰማኛል፣
ባንቀላፋሁበት…
እንደ ዶሮ ጩኸት፣
እንደ ደብር ደውል፣
እንደ ወፍ ዝማሬ፣ ይቀሰቅሰኛል።
የናፈቅከኝ ለታ…
የሞቀው አልጋዬ…
እንደ ምድር ዋልታ
እንደሙት ሰውነት
እንደደጋን ቆፈን ይቀዘቅዘኛል፣
ለስላሳው አንሶላ
እንደ ደረቅ ቁርበት ይኮሰኩሰኛል።
የተመቸው ነገር ምቾት አይሰጠኝም፣
የጣፈጠው ምግብ
ጣዕሙ አይገባኝም።
( ውሃ እንኳ ያንቀኛል።)
አይገርምም?!
የናፈቅከኝ ለታ…
ጨዋታው ለዛ ቢስ
ሙዚቃው ሁካታ
ፀሐይዋ በረዶ
ቅዝቃዜው እቶን ሆኖ ይሰማኛል፣
ከተፈጥሮ አጋጭቶ
ከሰውኛ ህግጋት ገፍቶ ያስወጣኛል።
የናፈቅከኝ ለታ…
የጨረቃ ውበት አይስብ አይማርከኝ
የከዋክብት ብርሃን ከሉን አይገፍልኝ
ብቻ አንተን ብቻ አንተን አንተን እላለሁኝ።
ዳሩ ምን ዋጋ አለው…
ፀጉርህን ዳብሼ አቅፌ እንዳልስምህ
ድምፅህን እንዳልሰማ ናፍቄ እንዳላይህ
እልፍ ርቀኸኛል!
ህልም ሆነህብኛል!
ቢሆንም…
ወድሃለሁና ትናፍቀኛለህ
በሠዓት በደቂቃ ትዝ ትለኛለህ።
`ወድሃለሁና እናፍቅሃለሁ
ያውም ደስ እያለኝ፣
ተስፋ አለኝ ባንተ ደርሰህ እስክታክመኝ።
ደግሞ…እጠብቅሃለሁ!
ተከተይኝ በለኝ…
እስከዓለም ጥግጋት…
እስከዓለም ፍፃሜ…
ማቄን ጨርቄን ሣልል…እከተልሃለሁ!
ትናፍቀኛለህ…ውዴ…እወድሃለሁ!
* Mes Demoze
( ጥር 21 ቀን 2005 ዓ.ም)

